ዜና | Oduu | News
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ትራንስፓርት ቅ/ጵ/ቤት ቢሮውን በዘመናዊ መንገድ ሰርቶ አስመርቋል።

በትራንስፓርት ዘርፍ አመስጋኝ ማህበረሰብ ለመፍጠር በሚደረግ ሂደት የስራ ቦታን ምቹ ማድረግ አንዱ ተግባር ነው። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ትራንስፓርት ቅ/ጵ/ቤት ቢሮውን በዘመናዊ መንገድ ሰርቶ አስመርቋል። ቢሮውን የመረቁት የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢር ኃላፊ አቶ ያብባል አዲስ ባደረጉት ንግግር፤ የትራንስፓርት ዘርፉን ለማዘመን ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ትራንስፓርት ቅ/ጵ/ቤት ቢሮውን በአዲስ ከመስራትና ለስራ ምቹ እንዲሆን ከማድረጉ ባሻገር ዘመናዊነትን የተላበሰ አሰራር ለመከተል ዌብሳይት በመክፈትና ካሜራዎችን በየቦታው በመትከል የሰራው ስራ ለሁሉም ፅህፈት ቤቶች አርዓያ መሆኑን ገልፀዋል። በተለይም የንፋስ ስልክ ላፍቶ ትራንስፓርት ቅ/ጵ/ቤት "ፅዱ አዲስ ትራንስፓርት" በሚል ያስጠናው ፁሁፍ በከተማ ደረጃ ተግባራዊ ይሆናል ብለዋል። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ትራንስፓርት ቅ/ጵ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሱራፌል ባያብል በበኩላቸው፤ ዘርፉን ተመስጋኝ ለማድረግ በትብብር ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ትራንስፓርት ቅ/ጵ/ቤት ቢሮ በሁለንተናዊ መልኩ ታድሶ ተመርቋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ገመገመ፡፡

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስራ አስኪያጆች እና ከማዕከል ዳይሬክተሮች ጋር በመሆን በበጀት ዓመቱ ባለፉት ሶስት ወራት በዕቅድ የያዛቸውን እና ያከናወናቸውን ተግባራት ገምግሟል፡፡ በበጀት ዓመቱ ሶስት ወራት ተቋማዊ የማስፈጸም አቅም፤ የአገልግሎት አሰጣጥ፤ የመልካም አስተዳደር እና የሀብት አጠቃቀም በማጎልበት ፣የትራንስፖርት መሰረተ ልማትን በማስተዳደር፣የህዝብ እና ጭነት ትራንስፖርት አቅርቦትና አገልግሎት በማሳደግ፣የስትራቴጅክ ጥናት እና የዘርፉን የቴክኖሎጂ አቅም በማጠናከር ዙሪያ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱን አስታውቋል፡፡ የሪፎርም ስራ ላይ ትኩረት ተሠጥቶ መሰራታቸው፣ከተቋማትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ ስራዎች መጠናከራቸው፣የህዝብ ትራንስፖርት አቅርቦትና አገልግሎት መሻሻላቸው፣የብዙሃን ትራንስፖርት ማጓጓዝ ድርሻ ዕቅድ መሳካታቸው፣የክትትልና ድጋፍ ስርዓታችን መሻሻላቸው፣የኮሚኒኬሽን ስራዎቻችን የዘርፉን ሥራዎችና እንቅስቃሴዎች ያጎላ መሆኑ፤የተለያዩ የክረምት በጎ አድራጎት፣የእንሼቲቭ ሥራዎችንና የ90 ቀን ዕቅድ በአግባቡ ውጤታማ በሆኑ መልኩ ማከናወናቸው በጥንካሬ ተነስተዋል፡፡ በቀጣይነትም የሪፎርም ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ስራዎችን በስታንዳርድ መሰረት እንዲከናወኑ ማድረግ፤የምሽት ትራንስፖርት አገልግሎትን ማሳደግ፤የህዝብ ትራንስፖርት የስምሪት ስርዓትን የማሻሻል ስራ ላይ የተለየ ትኩረት ማድረግ፡፡በሌብነትና ክራይ ሰብሳቢነት ላይ ትኩረት በማድረግ እርምጃ የመውሰድ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም በግምገማው ወቅት ተጠቅሷል፡፡

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
‹‹በሩብ ዓመቱ የታዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ስኬታማነትን ማስቀጠል ይገባል፡፡›› አቶ ያብባል አዲስ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የአንደኛው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ከአመራርና ባለሙያዎች ጋር በገመገሙበት ወቅት እንደተገለፀው የከተማዋን የትራንስፖርት ሂደት ተደራሽ፣ አስተማማኝ፣ ምቹ፤ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ከባቢያዊ ተስማሚነቱ የተረጋገጠ ለማድረግ በርካታ ተግባራት እተከናወኑ እንደሚገኙ ተገልፅዋል፡፡ የቢሮ ሃላፊ አቶ ያብባል አዲስ እንተናገሩት በሩብ ዓመቱ ከታዩ ስኬታማ ስራዎች መካከል የበጎ አድራጎት እና ኢኒሼቲቭ ስራዎች ፣የአደረጃጀትና አሰራር ተግባራት፣የመመሪያ እና ደንብ ዝግጅቶች፣የፍላጎት እና አቅርቦት የማመጣጠን የተጀመሩ ስራዎች፣የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ተግባራት፣የተካሄዱ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች፣አሮጌ ተሸከርካሪዎችን በአዲስ ለመተካት የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ስራዎችን በማስቀጠል እና ተግባራትን በላቀ ሁኔታ በመፈፀም በሁለተኛው ሩብ ኣመት ዋንኛ የዕቅድ መተግበሪያ ጊዜ ማድረግ እንደሚገባ አሳታውቀዋል፡፡ የቢሮ የፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዋሲሁን ታረቀኝ በበኩላቸው የታየውን የተሻለ የዝግጅት ምዕራፍ ከግምት በማስገባት በቀጣይነት ከመረጃ አያያዝ ፣ከሪፎርም ስራዎች፣ከአገልግሎት አሰጣጥ፣ከሰው ሃይል ስምሪት፣ከበጀት አጠቃቀም እና ፋይናንስ፣ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት አንፃር ትኩረት በማድረግ በተሻለ መልኩ መፈፀም እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቅርንጫፍ ትራንስፖርት የአራት ወር አፈፃፀም ገመገመ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቅርንጫፍ በትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ "አመሰጋኝ ማህበረሰብ መፍጠር" በሚል መርህ ሀሳብ ሲያከናውን የነበረውን የአራት ወር አፈፃፀም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ገምግሟል። በአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው እና የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሱራፌል ተቋሙ አመሰጋኝ ማህበረሰብ መፍጠር" በሚል መርህ ሀሳብ ሲያከናውን የነበረውን የአራት ወር አፈፃፀም ሰፊ ውይይት አድርገዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፉ አመሰጋኝ ማህበረሰብ የመፍጠር ሂደት የባለሙያ ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቅርንጫፍ በትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ አመሰጋኝ ማህበረሰብ የመፍጠር ሂደት ውስጥ የባለሙያዎች ሚና የላቀ እንደሆነ ተገለፀ። በአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሱራፌል ባያብል ከባለሙያዎች ጋር አገልግሎት አሰጣጥ፣ ሪፎርም እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ ከባለሙያዎች ጋር ውይይት አደረጓል

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በቢሮው እና በሸገር ከተማ ትራንስፖርት ፅህፈት ቤት መካከል ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የህበረተሰቡን እርካታ ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ እና በሸገር ከተማ ትራንስፖርት ፅህፈት ቤት መካከል የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡን በማጠናከር ፣ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት እና የተናበበ የትራንስፖርት ስርዓትን በመዘርጋት የህብረተሰቡን እርካታ ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገላፀ፡፡ በቢሮ እና በፅህፈት ቤቱ መካከል የ2018 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የጋራ ዕቅድ አፈፃፀምን በሸገር ከተማ መልካ ኖኖ ክፍለከተማ በገመገሙበት ወቅት እንደተገለፀው በትራንሰፖርቱ መስክ የሚስተዋሉ ችግሮችን እና የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በጋራ ተቀናጅቶ በመፍታት የተገልጋዩን እርካታ የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል ይገባቸዋል፡፡ በውይይቱ በአንደኛው ሩብ ዓመት በቅንጅታዊ ስራ የታዩትን ውጤታማ ተግባራት በተለይም ህገወጥ የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በመቆጣጠር፣የምሽት ትራንስፖርትን በማጎልበት፣የብዙሃን ተደራሽነትን በማስፋፋት፣የተቀናጀ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ፣የስምሪትና ቁጥጥር ስርዓትን ወጥነት በመተግበር እና በማጠናከር፣አቅርቦትንና ፍላጎትን በማጣጣም ዙሪያ በመናበብ እና በጋራ ቅንጅታዊ ስራ በመስራት የህብረተሰቡን እንግልት በመቀነሰ የትራንስፖርቱን መስክ እርካታ ማረጋገጥ እንደሚገባ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ውይይቱን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራውና የሸገር ከተማ ትራንስፖርት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያሲን አህመድ መድረኩን በጋራ የመሩ ሲሆን የቢሮ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆችና የሸገር ከተማ ትራንስፖርት ፅህፈት ቤት የክፍለከተሞቹ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
"በትጋት ዜሮ ቅሬታ ፤ ዜሮ ህገወጥ አፈፃፀም ይመዘገባል" - አቶ ሱራፌል ባያብል

በትራንስፖርት ዘርፍ የሚሰጠው አገልግሎት ላይ ዜሮ ቅሬታና ዜሮ ህገወጥ አፈፃፀም እናስመዘግባለን። በአዲስአበባ ትራንስፖርት ቢሮ ን/ስ/ላፍቶ ቅርንጫፍ በትራንስፖርት ዘርፉ በሚሰጡ አገልግሎቶች በትጋት ዜሮ ቅሬታ ፤ ዜሮ ህገወጥ አፈፃፀም ለማምጣት የሚያስችል የሚያስችል ውይይት ተካሂዷል። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሱራፌል ባያብል የትራንስፖርት ዘርፉ ላይ የላቀ አገልግሎት በመስጠት ምንም ቅሬታ የማይቀርብበትና ምንም ህገወጥ የሌለበት አፈፃፀም ለማምጣት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ከጅኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ተሻለ ቁመና በሚል መሪ ሃሳብ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር ውይይት ተካሄደ ።

በአዲስአበባ ትራንስፖርት ቢሮ ን/ስ/ላፍቶ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት "ከጅኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ተሻለ ቁመና" በሚል መሪሃሳብ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ጋር ውይይት ተካሂዷል። የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሱራፌል ባያብል ኢትዮጵያ ያሏትን ተፈጥሯዊ ጸጋዎቿን በመጠቀም ከነበረችበት የኩስመና ጊዜ ተላቃ ወደ ተሻለ ጅኦስትራቴጂካዊ ቁመና የመሸጋገር አገራዊ ብልፅግና ላይ እንደምትገኘና ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር በር ተጠቃሚነት በራሷ ዜጎች የተገለለችበትን እኩይ ሴራ በአለም አቀፍ ህግ የባህር በር ባለቤትነት የምንመልስበት ጥያቄ በማቅረብ በብዙዎቹ የአለም አገራት ተቀባይነት እያገኘች በመሆኑ የባህር በር ጥያቄ ሁሉም ዜጎች ሊደግፉት እንደሚገባ ገልፀዋል። የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ በመያዝ ለሁለንተናዊ ብልፅግና እውን መሆን ሁላችንም የሚጠበቅብንን እንወጣለን ሲሉ ተናግረዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
‹‹በትራንስፖርት ዘርፍ አመስጋኝ ማህበረስብ እንፈጥራለን!›. በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ተካሄደ፡፡

በአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አዘጋጅነት የትራንስፖርት ዘርፉን በማዘመን በተሰሩት እና በሚሰሩ ስራዎች የሚያመሰግን ማህበረሰብ እንፈጥራለን በሚል ዕሳቤ ሁሉን አቀፍ የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡ በውይይቱ መክፈቻ ላይ የቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው እንደገለፁት ከተማዋ በፈጣን የልማት ግስጋሴ ውስጥ እንደመገኘቷ መጠን የትራንስፖርት ዘርፉን ተደራሽ፣ምቹ፣ከባቢያዊ ተስማሚነቱ የተረጋገጠ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ሊሆን ይገባዋል፡፡ በዘርፉ አመስጋኝ ህብረተሰብን ለመፍጠር እንዲያስችል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት አቶ ዳኛቸው በመሰረተ-ልማት ዝርጋታዎች፣በተሸከርካሪ ጥራት፣በቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት፣በአቅርቦት፣የትራፊክ አደጋን በመቀነስ እና ሌሎች ትኩረት በሚሰጥባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ቢሮው ጠንክሮ እየሰራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ በቢሮው የንፋስ ስልክ እና ላፍቶ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሱራፌል ባያብል በበኩላቸው ከተማዋ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ተመራጭ ከማድረግ አኳያ እየተሰሩ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልፀው ውይይቱ በትራንስፖርቱ መስክ የጎደለውን በማሟላት የታዩትን ጥንካሬዎች በማስቀጠል ውጤታማ ተግባር ለመፈፀም እና የሚያመሰገን ማህበረሰብ ለመፍጠር እንደሚያስችልም አስታውቀዋል፡፡ በውይይቱ ‹‹ትራንስፖርትና ከተሜነት›› በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በተጋበዙ እንግዳ ጥናታዊ ፅሁፍ የቀረበ ሲሆን ‹‹አዲሷ አዲስ አበባና ትራንስፖርት›› በሚል ሀሳብም ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ እና ከቅርንጫፍ ፅሀፈት ቤት አመራሮች እና ባለሙያዎች፣ከክፍለከተማ አመራሮች፣አባገዳዎች፣አሽከርካሪዎች፣ማህበራት፣የተርሚናል ኢንተርፕራይዞች፣ከተለያዩ አካላት የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተካፋይ ሆነዋል፡፡

image
image
image
image